ᴇʟɪᴀꜱ ᴍᴇꜱᴇʀᴇᴛ Profile picture
Founder/Editor @MeseretMedia @EthiopiaCheck Journalist-at-large, former @AP reporter in Ethiopia
Jun 9, 2022 5 tweets 1 min read
በአፋር ክልል ድርቅ፣ ጦርነት እና ስደት ያስከተለው የምግብ እጥረት የህፃናትን ህይወት መንጠቅ ጀምሯል። MSF ባለፉት 8 ሳምንታት ብቻ 35 ህፃናት ህይወታቸው እንዳለፈ ዛሬ ይፋ አርጓል፣ እኔም ከዱብቲ ሆስፒታል ዛሬ ያገኘሁት መረጃ ይህንኑ ያሳያል። "በማህበረሰቡ ላይ ስራ ካልተሰራ ህፃናት መሞት መቀጠላቸው አይቀርም። ሆስፒታሉ ሞልቶ ድንኳን ጥለን ነበር፣ አሁን እሱ ሞልቶ ኮሪደር ላይ ህክምና ለመስጠት እየሞከርን ነው። እጅግ ልብ ሰባሪ ሁኔታ ነው" ያሉኝ በሆስፒታሉ የሚገኙ አንድ ሀኪም ናቸው።