Naty Berhane Yifru Profile picture
Oct 18, 2020 49 tweets 8 min read Read on X
Thread 1
ኢትዮጵያና ወደብ፣
ብዙዎች ለኢትዮጵያ የባህር በር ተፈጥሮአዊ መብት መሆኑንና አለመሆኑን ሙግት ይገጥማሉ። የዚህ ቅጥልጥል አላማ ሙግቱን የመዳኘት ሳይሆን ፣ በኢትዮጵያ ወደብ አጠቃቀም ዙርያ አስገራሚና የተሸፈኑ እውነታዎችን ለማጫወት ነው
Thread 2
አዱሊስ፣
የወደብ ጥቅም በተደራጀ መልኩ በዛሬዋ ሀገራችን ጥቅም ላይ መዋል የጀመረው በአክሱማዊያን ነው። አክሱማዊያንና ከነሱም በፊት የነበሩት የዳማት ልዑላን በአዱሊስ መጠቀምን የመረጡት በወቅቱ ገናና በነበሩ ግሪካዊያንና ባዛንታይን..
Thread 3
..ነገስታት ለመገናኘትና የእጣን፣የወርቅ ፣የከበሩ ድንጋዮች፣ የአደን ዱር አራዊት ቆዳ ምርቶቻቸውን ከነዚሁ ነገስታት ጋር ለመገበያየት ቅርበቱ ያመቻቸው ስለነበረ ነው።
"አዱሊስ" (Άδουλις)የሚለው ቃል ሳይቀር የአካባቢው ሳይሆን ግሪካዊ ነው
Thread 8
ምጽዋ (ባፅእ)
..ከ8ኛው ክፍለ ዘመን አንስቶ በአካባቢው ቀስ በቀስ ስር የሰደደው የኦቶማን ቱርክ ገዛዔ-ኩሉሽ (Empire) ለግዛት ቅኝት ምቹ ቦታን በጥንቃቄ መርጦ የመስፈር ብልሀት ያለው በመሆኑ በጊዜው አነስተኛ መንደር በነበረችው ምጽዋ ሰፈረ።
Thread 9
በአካባቢው ይኖሩ የነበሩት የቤጃ ህዝቦች በመንደሪቱ አነስተኛ የከተማ መንግስት (city state) አቋቁመው ቀደም ብሎ ከአክሱም ከዚያ በሁዋላ ከአዲስ መጤዎቹ ተርኮች ጋር የገበያ ልውውጥ ያደርጉ ነበር። ይሁንና ከቱርኮች እየተጠናከሩ መምጣት ጋር
Thread 10
..ተያይዞ የከተማ መንግስታቸው አደጋ ላይ ወደቀ። ከተለያዮ በአቅራቢያው ከሚገኙ ቃታ፣ባቅሊን እና ዳህላክ ከሚባሉ አነስተኛ ጎሳዎች ጋር ህብረት በመፍጠር ህልውናቸውን ለማስጠበቅ ቢሞክሩም እጅግ ግዙፍና ዘመናዊ የነበረውን የኦቶማን ቱርክን
Thread 11
..ኃይል መቋቋም ስላቃታቸው ትንሿ የባህር ዳርቻ መንደራቸው ከቁጥጥራቸው ውጭ ወጣች። ኦቶማኖች ሙሉ በሙሉ አካባቢውን ከተቆጣጠሩ በሁዋላ ምጽዋን የተቀሙበት ባብዛኛው የደቡባዊ ቀይባህርን እንደ ቅኝት መቃኛ እንጂ ለወደብነት አልነበረም።
Thread 12
ይሁንና ከአክሱም መዳከም በሁዋላ በዛሬው ሰሜናዊ ኢትዮጵያ የተቋቋሙት መንግስታት ታላቁን የዛግዌ ስርወ መንግስት ንጉስ ላሊበላን (ገብረመስቀል) ጨምሮ የምጽዋን ወደብነት እንደሚፈልጉት ስለተገነዘቡ እንደ የተለያዩ ፓለቲካውና ሃይማኖታዊ
Thread 13
ፍላጎታቸው መያዣና ማስገደጃነት መጠቀም ጀመሩ። ለምሳሌ ንጉስ ላሊበላ ወደ ኢየሩሳሌም እንደልብ መመላለስ ህልም በዚሁ ምክንያት እክል ስለገጠመው ነበር አዲሲቱን ኢየሩሳሌም በኢትዮጵያ ለመገንባት የሻተውና የላሊበላን አብያተ ክርስቲያናት
Thread 14
..የገነባው ብለው በርካታ ታሪክ ጸሐፊዎች ጽፈዋል። ኦቶማን ቱርኮች ምጽዋና አካባቢውን እንደ ጦር ካምፕና ወደሌላው የቀይ ባህርና ህንድ ውቅያኖስ የሚያዘምቱት ወታደር መመልመያ ይጠቀሙበት ስለነበር በርካታ ህንጻዎችን ገንብተዋል።

Thread 17
ይህንን የተገነዘቡት ኦቶማን ቱርኮች በተለያየ መንገድ ሞክረው ኢትዮጵያን በነሱ ሀይማኖታዊና ፖለቲካዊ ተጽእኖ ስር ለማሳደር የሚያደርጉትን ጥረት በመቀጠል በአካባቢው የነበሩትን የሶማሌ ባላባቶች የሀይማኖትና የጎሳ መሪዎችን
Thread 20
..ክፍለ ዘመን መጨረሻ ቆይተዋል። በዚህ ሁሉ ዘመን ከባህር ጠረፍ እቃዎችን በማመላለስና የባህር ንግድን በማሳለጥ የአርጎባና የአፋር ነጋዴዎች (በጊዜው አዳል ተብለው ነበር የሚጠሩት) ህዝቦች ያደረጉት አስተዋጽኦ ተስተካካይ አልነበረውም
Thread 21
በርበራና ታጁራ
ከ18ኛው ክፍለዘመን ጀምሮ ፣ በተለይ የአሁኑ ምስራቅ ኢትዮጵያ ክፍል ሐረር በማእከላዊ መንግስት ቁጥጥር ስር ከዋለ በሁዋላ የዛሬዋ ሶማሌላንድ 2ኛ ከተማ በርበራና በጊዜው በፈንሳይ ኩባንያ ስር የነበረው የአሁኑ ሰሜናዊ ጅቡቲ
Thread 22
..የወደብ ከተማ ታጁራ ለኢትዮጵያ የወደብ አገልግሎት መስጠት ጀመሩ። ይሁንና በታጁራ እጅግ ሞቃታማ ያየር ጠባይ የተነሳ የፈረንሳዩ ኩባንያ ንብረቱን ለጅቡቲ መንግስት በመሸጡና ከኢትዮጵያ ጋር የነበረውን ግኑኝነት በማቋረጡ..
Thread 23
..በርበራ ደግሞ ቀዝቀዝ ባለው የአየር ጠባዮ ምክንያት የነጋዴዎች ምርጫ በመሆኑ አብዛኛው ንግድ በዚያው ቀጥለ። የፈረንሳይ መንግስት ብዙም ሳይቆይ ከኩባንያው የገዛውን ታጁራን ትቶ በኤደን ባህረ ሰላጤ ለቅኝት አመቺ የሆነችውን
Thread 24
..የኦቦክ (በሁዋላ ጅቡቲ) መንደር ለመቀመጫነት ሲመርጥ ዳግማዊ ዓፄ ምኒሊክ መንደሯን ለወደብነት ለመጠቀም ከፈረንሳይ መንግስት ጋር ስምምነት አደረጉ። ምንም እንኳን በተቀዛቀዘ መልኩ ቢሆንም ከሳቸው በፊት ኢትዮጵያን የመሩት
Thread 25
ዓፄ ዮሐንስ 4ኛ የኢትዮጵያን ቀድሞ በምጽዋ ወደብ የመጠቀምን ሁኔታ ለማመቻቸት ቢሞክሩምና የጦር አዛዣቸውን ራስ አሉን አካባቢውን እንዲቆጣጠሩ ደጋግመው ቢልኩና አንዳንድ የንግድ እንቅስቃሴዎች ቢደረጉም በምጽዋ በኩል በእሳቸው ዘመን
Thread 26
..በምጽዋ በኩል ግብጾች ፣ ደርቡሾችና ኢጣልያኖች ኢትዮጵያን ለመወረር በሚያደርጉት ሙከራ እንደ በር የሚጠቀሙበት ስፍራ በ መሆኑ እነሱን ለመመከት ፍልሚያ የሚደረግበት የብሔራዊ ስጋት ምንጭ የነበረ ስፍራ ነበር።

Thread 27
ዳግማዊ ምኒሊክ በኢትዮጵያ የወድብ አጠቃቀም ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ከፈረንሳይ ጋር ባደረጉት ስምምነት የቀድሞዋን ኦቦክ መንደር ሁዋላ ጅቡቲ የተሰኘችውን በሚገባ ተጠቀሙባት። የኢትዮጵያ ዋና ወደብ በመሆኗም የባቡር መስመር ሳይቀር
Thread 28
..አስገነቡ። ዳግማዊ ምኒሊክ በፈረንሳይ ነጋዳዎች ዘንድ "ለንግድ ስራ የተመቹ ዘመናዊ አፍሪካዊ መሪ ናቸው" ብለው ያስቧቸው ነበር። ታዋቂነታቸው እስከ ዛሬ ዘልቆ በጀቡቲ መሐል ከተማ "ምኒሊክ ሆቴል" የሚባል ቆየት ያለ ህንጻ አለ
Thread 29
ጋምቤላ ወደብ
..ዳግማዊ ዓፄ ምኒሊክ የደቡብንና ደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያን ወደ ማእከላዊ መንግስት ሲያጠቃልሉ በባሮ ወንዝ ላይ ያለ የእቃ ማራገፍያ ስፍራ በጊዜው ሱዳንን ይገዙ የነበሩት እንግሊዞች ሲጠቀሙበት አስተዋሉ።
Thread 30
..ጠቀሜታውን በፍጥነት የተገነዘቡት ዓፄ ምኒሊክ ቦታው የኢትዮጵያ ድንበር ውስጥ መሆኑን ለእንግሊዞቹ አስረግጠው ፣ ለአገልግሎቱ ክፍያ ጠይቀው ተቀበሉ። ይሁንና ከቦታው ርቀት የተነሳና ከዋና ወደብ 1366 ኪሎ ሜትር በመራቁ ከእንግሊዞቹ
Thread 31
..የአገልግሎት ቀረጥ ከመሰብሰብ ባሻገር እምብዛም ለኢትዮጵያ የውጭ ንግድ አልተጠቀሙበትም። ይሁንና የጅማውን ንጉስ አባ ጅፋርን በቅርብ እንዲቆጣጠሩትና የሚጠቀሙበትም ነገር ካለ እንዲጠቀሙ ሀላፊነቱን ሰጧቸው።
Thread 32
አባ ጅፋር ቡና የዝሆን ጥርስ እና የዱር እንስሳት ቆዳ በዚህ ወደብ ተጠቅመው ለእንግሊዞቹ በመሸጥ ከፍተኛ ገቢ ያገኙ ነበር። ከዚሁ የተገኘውንም ሀብት ለራሳቸው የሚሆነውን አስቀርተው ወደ አዲስ አበባ ለዳግማዊ ምኒሊክ ይልኩ ነበር።

Thread 33
ነገር ከትንሽ ቆይታ በሁዋላ እንግሊዞቹ አባ ጅፋርን በዚሁ ወደብ ባርያ ለመሸጥ ይጠቀሙበታል ብለው ስለከሰሱዋቸውና ዐፄ ምኒሊክ በዚህ እጅግ ተቆጥተው በወደቡ እንዳይጠቀሙ ከልክለዋቸው ነበር። ነገር ግን ከዓፄ ምኒሊክ ህልፈት በሁዋላ
Thread 34
ልጃቸው ኢያሱ 4ኛ ሲተኩ የተከለከሉቱን የወደብ ንግድ ለአባ ጅፋር መልሰው ፈቀዱላቸው። ይህ በእንዲህ ኢጣልያ ኢትዮጵያን እስክትወር ቆይቶ ሙሶሎኒ በጊዜው ሱዳንን ከምታስተዳድረው እንግሊዝ ጋር በነበረው መቃቃር ይህ ወደብ ምንም ጥቅም
Thread 35
እንዳይውል ተከለከለ። ነጻነትም ከተመለሰም በሁዋላ ወደቡ እንደ ቀረጥ ጣቢያ ሲያገለግል ከቆየ በሁዋላ ከጥቅም ውጭ ሆኖ ቆይቶ ወታደራዊው መንግስት ደርግ ለደቡብ ሱዳን አማጽያን መሳርያ ለማስታጥቅ ይጠቀምበታል ተብሎ በአለምአቀፍ...
Thread 36
..ማህበረሰብና አንዳንድ አረብ ሀገራት ክስ በመብዛቱ በ1983 እንደ አውራፓውያን አቆጣጠር ሙሉ በሙሉ ተዘጋ። በኢህአዴግ አስተዳደር ዘመን እንደገና አገልግሎት እንዲሰጥ የተደረገ አነስተኛ ጥረት ቢኖርም አሁንም ካገልግሎት ውጪ ነው።
Thread 37
የአሰብ ወደብ
አሰብ በደቡባዊ ቀይ ባህር ጫፍ የሚገኝ ቀደም ባሉት ዘመናት እምብዛም በወደብነቱ የማይታወቅ፣ ነገር ግን በጣም ሰፊና በተንጣለለ የባህር ዳርቻ የሚገኝ ወደብ ነው። ከሳምንታት በፊት በጻፍኩት ቅጥልጥል ይህ ቦታ በኢትዬጵያዊው..
Thread 38
አዳል ሱልጣን ይተዳደር የነበረ የአፋር የአርጎባ ህዝቦች መኖርያ ስፍራዎች አንዱ ነው። አፋሮች ይህንን ቦታ ከባህር ማዶ ካሉት የየመን ሐድራሙት ጎሳዎች ጋር የንግድ ልውውጥ የሚያደርጉበት ስፍራ ነበር። ቦታው እጅግ ሞቃታማና ለኑሮ የማይመች
Thread 39
..በመሆኑ ነጋዴዎች እምብዛም ለንግድ ስራ አይመርጡትም። እስከ 18ኛው ክፍለዘመን አጋማሽ ድረስ ብዙ አልፎ ሂያጆች በጽሁፋቸው ጠቀስ ከማድረጋቸው በቀር አብዛኛውን ጊዜ የዚህ ቦታ ታሪክ የሚነሳው ከአፋር ህዝቦችና አዳል ሱልጣኔት ጋር ተያይዞ
Thread 40
ብቻ ነው። የአሰብ ነገር መጉላት የጀመረው በ1830 እራሱን የካቶሊክ ቄስ ነኝ ብሎ የሚጠራ በሁዋላ ግን ብዙዎች ካህንነቱን የሚጠራጠሩት ጁሰፔ ሳፔቶ የተባለ ኢጣልያዊ ባካባቢውና በሰሜን ኢትዮጵያ ከመጣ ጀምሮ ነው።
Thread 41
ሳፔቶ ከመጣበት የ"ቅስና" ስራ ውጪ ለተለያዮ የኢጣልያ ኩባንያዎች እንደ ወኪል ሆኖ መሬት በመግዛት ተጠምዶ ነበር። በዚህም መሰረት ነበር በጊዜው የአዳል (አፋር) ስልጣን ከነበሩት ስልጣን ኢብራሒም አሰብንና አካባቢውን የገዛው።
Thread 42
ምንም እንኳን የዚህ ግዢ አፈጻጸምና መፈጸሙም እራሱ በተለያዩ የታሪክ ጸሐፊዎች አወዛጋቢ ቢሆንም ፣ የኢጣልያ መንግስት ለሩባቲኖ የእቃ ጫኝ ኩባንያ (Rubattino shipping company) የ6ሺ ማርያቴሬዛ ሽያጭ አጸደቀ።
Thread 45
የጦር መሳርያ ለማስገባት ተጠቅሞበታል።
ኢጣልያ በጦርነት ተሸንፋ ከኢትዮጵያና የዛሬዋ ኤርትራ ስትባረርና እንግሊዞች ኤርትራን በሞግዚትነት ሲያስተዳድሩ ፣ ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት ስለ ኤርትራ የወደፊት እጣ ፈንታ ካቀረቡት ሀሳብ
Thread 46
አንዱ አሰበንና የኤርትራን ደገኛ ክፍል ለኢትዬጵያ አስቀርቶ የኤርትራን ቆለኛ ክፍል ከሱዳን መቀላቀል ነበር። ሆኖም ነጻነት ፈላጊዎቹ የኤርትራ ቆለኛ ፖለቲከኞችም ሆኑ ከኢትዮጵያ ጋር ፌዴሬሽን ወይም አንድነት ፈላጊዎች ደገኛ ኤርትራዊያን
Thread 47
እና የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተወልድ ኤርትራን የመከፋፈሉን ሀሳብ እጅግ አድርገው ስለተቃወሙት ሀሳቡ ውድቅ ሆኖ ቀረ። ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር በፌዴሬሽን ስትቀላቀል ፣ ቀዳማዊ ሀይለስላሴ "የወደብ አስተዳደር መስርያ ቤት"
Thread 48
በሚል ተቋም አቋቁመው አሰብ ወደብን የወደብ ቁመና እንዲይዝ ስራው ተጀመረ። ይሁንና 90 በመቶ የሚሆነው የኢትዮጵያ የወደብ አገልግሎት ይከናወን የነበረው በምጽዋ ወደብ ነበር። ምጽዋ ኢጣያዊያን ለራሳቸው የቅኝ ግዛት ጥቅም አሳምረው..
Thread 49
የሰሩት ወደብ በመሆኑ እነሱ ትተውት የሄዱት መሰረተ ልማት የተሻለ ሆኖ በመገኘቱ ኢትዮጵያ የባህር ሀይሏንም በዚያ አቋቋመች። ይሁንና አሰብም ቢሆን መጠነኛ መሻሻል ዘመናዊ አስተዳደርና የንግድ እንቅስቃሴ ማየት ጀምሮ ነበር።
Thread 52
አጠናክሮ ቀጥሎ ድፍድፍ ነዳጅ እያጣራ ወደ መሀል ሀገር ይልክ ነበር። አሰብ በርካታ ኢትዮጵያዊያን ከመሀል ሀገር ሄደው የሚኖሩበትና የአማርኛ ቋንቋ እንደዋነኛ መግባቢያ የሚነገርባት ሞቅ ያለች ሆና ነበር።
በ1983 ኢህአዴግ አዲስ አበባን
Thread 53
ሲቆጣጠር በአሰብ ቁጥሩ ቀላል የማይባል የቀድሞው የኢትዮጵያ ሰራዊት ሰፍሮ ነበር። ይሁንና የዚያን ጊዜው የሽግግር መንግስት አሰብን የኤርትራ ሉዐላዊ መሬት ነው የሚል ግትር አቋም በመያዙና የተለየ ሀሳብ ያላቸውን ኢትዮጵያዊያን ሁሉ...
Thread 54
ጦርነት ፈላጊ ጸረ ሰላም በሚል በማግለሉ በጊዜው በአሰብ ይኖሩ የነበሩ በርካታ ኢትዮጵያዊያን አስመራን ከተቆጣጠረ ከሳምንታት በሁዋላ አሰብ በዘለቀው የሻእቢያ ጦር አሳዛኝ እንግልት ደርሶባቸው ተባረሩ
Thread 55
እነዚሁ ዜጎች ለበርካታ ወራት ከላስቲክና ከጨርቅ በተሰራ የጎዳና መጠለያ በደሴና በአዲስ አበባ ጃን ሜዳ ሰፍረውን አሳዛኝ ኑሮ ይገፉ እንደነበር ከቶ የሚረሳ አይደለም። ይህንን ዛሬም ድረስ በህይወት ያሉ ወይም ልጆቻቸው ያስታውሱታል።
Thread 56
በአሁኑ ወቅት አሰብ ምንም አይነት የወደብ አገልግሎት የማይሰጥ፣ ፈጽሞ የንግድ እንቅስቃሴ የማይታይበት ፈረንጆች የመናፍስት ከተማ (Ghost City) የሚሉት እንደሆነ ይነገረል።
Thread 57
በቅርብ ጊዜ የኤርትራ መንግስት ለአረብ ኤምሬት የጦር አውሮፕላኖች የመንን ለማጥቃት ለሚያደርጉት ድብደባ እንዲጠቀሙበት እንደሰጣቸው ይነገራል። አሰብ ብቻ ሳይሆን የኤርትራም ዋና ወደብ ምጽዋ ይሄ ነው የሚባል የወደብ ስራ የማይታይበት
Thread 58
ቁጥሩ ከሀያ ሺ ያነሰ ነዋሪ ብቻ ያለበት ፣ እንደ ስልታዊ ቦታነቱ እንኳን ለአካባቢው ሀገራት እራሷን ኤርትራም ያልጠቀመበት ሁኔታ ነው ያለው። ኢትዮጵያና ኤርትራ ሰላማዊ ግኑኝነት ፈጥረዋል ከተባለ ሁለት አመታት ቢያልፉም
Thread 59
ከኤርትራው ፕሬዘዳንት ኢሳያስ አፈውርቂና ከኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እንደ ወግ ቀጂ በሁለቱ ሀገራት ዋና ከተሞች መካከል መመላለስ እንጂ እነዚህ ወደቦች ሊያመጡ በሚችሉት ፋይዳ ላይ እየተደረገ ያለ አንዳችም ነገር የለም
Thread 60
ይህ ቅጥልጥል እጅግ በመርዘሙ ይቅርታ እየጠይኩ ፣ አስተያየት ሰጪ ኢትዮጵያዊያንም ሆነ ኤርትራዊያን ሀሳባችሁን በጨዋነት ከመግለጽ በቀር ከግላዊ ስድብ ዘረኛ አስተያየት እንድትቆጠቡ አጥብቄ አሳስባለሁ።
ማረሚያ :- የኦቶማን ምጽዋንና አካባቢውን የተቆጠረው ከ1450 ጀምሮ መሆኑን ተጠቁሜአለሁ። ትክክል ነው። ይሁንና ተጽእኗቸው ከሌሎች የአካባቢው አረብ ሀይሎች ጋር ተዳምሮ ቀደም ብሎ ነው የጀመረው። @EndangeredE1987 @PreciseConsult በጣም አመሰግናለሁ 🙏

• • •

Missing some Tweet in this thread? You can try to force a refresh
 

Keep Current with Naty Berhane Yifru

Naty Berhane Yifru Profile picture

Stay in touch and get notified when new unrolls are available from this author!

Read all threads

This Thread may be Removed Anytime!

PDF

Twitter may remove this content at anytime! Save it as PDF for later use!

Try unrolling a thread yourself!

how to unroll video
  1. Follow @ThreadReaderApp to mention us!

  2. From a Twitter thread mention us with a keyword "unroll"
@threadreaderapp unroll

Practice here first or read more on our help page!

More from @NatyYifru

Jun 20, 2022
❗Thread 1/10
Here is why I believe the very large part of #Amhara/#Ethiopia political, religious media, academic, business, art elites continue to be a cause for innocent Amharas getting slaughtered all over #Ethiopia.

It starts with their toxic & dangerous politics.
❗Thread 2/10
Their toxic rhetoric, their idiotic alliances with elements, who're dangers to #Amhara people like #IsaiasAfwerki & @AbiyAhmedAli their unending love & nostalgia of medieval times kings & princes earned the #Amhara people enemies across #Ethiopia & made it a target
❗Thread 3/10
Its political "leaders" organize lawless bandits like 'Fano', and send them to all directions to wreck havoc on peoples of #Tigray #Gumuz #Oromia and made the people friend-less, ally-less and made #Amhara people target of unending attack.
Read 11 tweets
Jun 10, 2021
❗Thread 1/10
It is a depressing day for me!
To hear that #UN declared famine in #Ethiopia, on top of rape, murder, foreign invasion & wanton murder om #Tigray has been the most bitter pill to swallow.
❗Thread 2/10
As a very young, FOB in America, I remember watching 2000 Sydney Olympics, when Ethiopian athletes won their races, the broadcast cutting away to 1984/95 famine to remind viewers of the #Ethiopia they came from. My heart used to sink with embarrassment than joy.
❗Thread 3/10
During those days, I endured crude jokes about "famished Ethiopians", as if there is NOTHING more than that about a country and people, where I came from. That was also the time, #Ethiopia was invaded by the same man, #IsaiasAfwerki that's causing this misrey today
Read 11 tweets
Feb 21, 2021
Thread 1
#ኢትዮጵያ|ዊያን
#ተጋሩ|ን ፋሽስቶችን መመከት ጽናት ምስጢር ለመረዳት እዚህ የ #ትግራይ ብሔራዊ መዝሙር ላይ ያሉ ስንኞችን ተመልከቱና ተረዱ

ሀሩር ጸሀይ ንዳድ
ሞገድና በረዶ
ነፍስ ዉሀ ውሀ ብትል
ማጥ ውስጥ ብንከተት
ድንጋይ ብንንተራስ
Thread 2
ቤታችን በረሀ ቢሆን
ሌት ተቀን ብንጓዝ
ብንደክም ብንራብ
ብንከበብ መሬት ብትጠበን
ተባዩ ጠላታችን ስጋችን ውስጥ ዘልቆ ይግባ እንጂ
ስጋችን ላሞራ ይሁን ደማችን ይዋጅ እንጂ
አጽማችን ደቆ ይበተን እንጂ
መርዛማ ጋዝ ፋሽስታዊ ንዳድ
Thread 3
ሚሊዮን ጥይት ይዝነብብን እንጂ
ህዝባችን ሀይላችን ነው
የከበብንን ጠላት እንጋፈጠዋለን
መስዋእት መቁሰል ኪሳራ እንክፈል እንጂ
የከፋ መከራም ይድረስብን
መስመራችን ሀይላችን ነውና
ህዝባችን ሀያላችን ነውና
እናሸንፋለን✊
Read 4 tweets
Feb 19, 2021
Thread 1
A lesson to the barbaric #UnityForEthiopia club.
These are same people whose churches & mosques you desecrated, raped, murdered, looted. Yet, when #Tegaru capture mostly naive, child soldiers you sent to do these things, #Tegaru see them as what they are. Human beings.
Thread 2
These young people, have been driven to war for your fascistic goal & unquenchable thirst to rule over others. You forced them to kill their brothers, rape their sisters, desecrate their churches & mosques. You made them POW in their own country.
Thread 3
As you see in these clips, no matter how much your crimes are unspeakably fascistic and barbaric in #Tigray, your barbarism is not being paid in kind. Learn from these civilized folks you intend to destroy! #Ethiopia
Read 4 tweets
Feb 19, 2021
Dear @befeqe
Thread 1
It's important to learn from history of the world that fascists NEVER win. They wreck havoc. They kill (Oh boy! do they know how to kill?) But, there is NO WHERE in history, where they won. When they lose, they lose in a fantastically humiliating manner!
Thread 2
Just like only flag colors & Teddy Afro song brings your lot together, they loved symbolism (The Swastika, the lifting left hand high salute the flag etc.) That is because other than those emotion triggering trivial matters, there's very little that brings them together.
Thread 3
Their HUGE commonality was HATE! In the case of Nazis, for example it was the hate of Jews most of all. And they came up with all sort of "creative" way to murder & torture Jews. Just like you came up with horrific kind of rape, looting and murdering #Tegaru
Read 6 tweets
Nov 21, 2020
Thread 1
ኢትዮጵያ ነገ:-
ለብዙዎቻችንን ድንገቴ በሆነ ሁኔታ የዛሬ ሶስት ሳምንት ሀገራችን ኢትዮጵያ በግትርና በማን አለብኝ መሪዎቿ (በሁለቱም ወገን) የእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ ተዘፍቃለች። እንደ እኔ እምነት ይህ ጦርነት እንዳይሆን ማደረግ..
Thread 2
የሚቻልባቸው በርካታ መንገዶችና ያመለጡ እድሎች ነበሩ። ይሁንና ስለፈሰሰ ውሀ መብስልሰሉን ትተን ነገ በምን ሁኔታ ሀገራችንን መታደግ እንደምንችል መነጋገር ብንጀምር አስፈላጊ ነው ብዬ አምናለሁ።
Thread 3
የጦርነት ዋጋ:-
በአለም ላይ በተደረጉ ሁሉም ጦርነቶች እንደታየው መጀመርያም መጨረሻም ላይ በአካል በምጣኔሀብት በስነልቦና የሚጎዳ ሰላማዊ ህዝብ እንጂ ተፋላሚ ጦር አንጋቾች አይደሉም። በተለይ በዚህ ጦርነት ሙሉ ለሙሉ በሚባል መልኩ..
Read 24 tweets

Did Thread Reader help you today?

Support us! We are indie developers!


This site is made by just two indie developers on a laptop doing marketing, support and development! Read more about the story.

Become a Premium Member ($3/month or $30/year) and get exclusive features!

Become Premium

Don't want to be a Premium member but still want to support us?

Make a small donation by buying us coffee ($5) or help with server cost ($10)

Donate via Paypal

Or Donate anonymously using crypto!

Ethereum

0xfe58350B80634f60Fa6Dc149a72b4DFbc17D341E copy

Bitcoin

3ATGMxNzCUFzxpMCHL5sWSt4DVtS8UqXpi copy

Thank you for your support!

Follow Us!

:(